Terms and conditions ቅጽ 0003 የውል ስምምነት

 

ይህ የውል ስምምነት የተዘጋጀው እና የተፈፀመው በኢቲኬር የውበት መጠበቂያ ምርቶች ሽያጭ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አድራሻ አዲስ አበባ፡- ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 የቤት ቁጥር 174 የቢሮ ቁጥር 601 በሆነ ተመዝግቦ በኢትዮጵያ ህግ መሠረት በተቋቋመው ድርጅት ከዚህ በኋላ "ድርጅት" እየተባለ በሚጠራው እና

እራሣቸውን የቻሉ የምርት አስተዋዋቂዎች አቶ ወ/ሮ                                    አድራሻ                               ከዚህ በኋላ "ውል ተቀባይ/ ውል ተቀባይ " እየተባሉ በሚጠሩ መካከል የተፈፀመ ስምምንት ነው፡፡

 

  1. የምርት አስተዋዋቂው ህጋዊ አቋም፡፡

ለዚህ ውል አፈፃፀም ውል ተቀባይ  ከድርጅቱ ጋር ያለው ግንኙነት የቅጥርም ሆነ የሽርክና አለመሆኑን ሁለቱም ውል ተቀባይ  ወገኖች በመግባባት ከዚህ የሚከተለውን ተስማምተዋል፡፡

1.1. ውል ተቀባይ  የምርት ማስተዋወቅ ስራ ድርጅቱ ለሚያቀርበው ምርትና አገልግሎት ለመሥራት ተስማምቷል፡፡

1.2. ውል ተቀባይ  የድርጅቱን ስራ እና መልካም ስም በጠበቀ መልኩ የሚሠጠውን የምርት ማስተዋወቅ ስራ በትጋት ለመስራት ተስማምቷል፡፡

1.3. ውል ተቀባይ  የምርት ማስተዋወቅ ስራውን በሚያከናውንበት ጊዜ አስፈላጊውን የስራ ስነ-ምግባር በሙሉ ይከተላል፡፡

1.4. ውል ተቀባይ  የምርት ማስተዋወቅ ስራ የሚያከናውነው በመረጠው ጊዜ እና ቦታ ይሆናል፡፡

1.5. ውል ተቀባይ  ስራውን የሚሠራበትን ጊዜ ስራውን የሚሠራበትን ሁኔት፣ ስራውን የሚጀምርበት እና የሚያቆምበትን ጊዜ፣ የስራውን ሰዓት እና ቅድማ ተከተል እና ለውሉ አፈፃፀም ይረዳው ዘንድ የሚከተለውን የአሰራር ስልት በራሱ የመወሠን መብት አለው

1.6. ከድርጅቱ ስራ ጋር ተመሣሣይ ስራ ከማይሠሩ እና ተፎካካሪ ካለሆኑ ድርጅቶች ጋር ሁሉ ውል ተቀባይ  ይህ ውል ፀንቶ በሚቆይበት ጊዜ ከሌሎች ድርጅቶችም ጋር ተዋውሎ የመስራት መብት አለው፡፡

 

2.  ውሉ የሚቆይበት ጊዜ

ከዚህ በታች የውሉ ጊዜ ከማለቁ በፊት ውሉን ለማቋረጥና የሚቻልባቸው ምክንያቶች ተብለው ከተዘረዘሩት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ወይምንም ሁሉመ ካላጋጠሙ በቀር ይህ ውል በውል ተቀባይ  እና በውል ሰጪ  መካከል ላልተወሰነ ግዜ ፀንቶ ይቆያል፡፡

3.  ባለቤትነት

ሁሉም በውል ሰጪ ተዘጋጅተው የሚሰጡ የምርት ማስታወቂያና የሽያጭ ስልት የስልጠና አሰጣጥ መመሪያ፣ የንድ ምልክት እና ስያሜዎች እንዲሁም ተያያዥ ደጋፊ መሣሪያ/መገልገያዎች ለስራው አመቺነት ለውል ተቀባይ  የሚሠጡ ማናቸውም  የህመትና የንድፈ ሀሳብ ንብረቶች ባለቤትነት የውል ሰጪ  ይሆናል፡፡

4.  ሽርክና የሌለ ስለመሆኑ

ይህ ስምምነት ምንም አይነት የሽርክና ግንኙነትን አያቋቁምም፡፡ ውል ተቀባይ ውል ሰጪን በመወከል ከሌሎች ሶስተኛ ወገኖች ጋር ለመዋዋል የሚያስችል አይደለም፡፡

5.  የውሉ አፈፃፀም ክፍያ

ውል ተቀባይ የውል ሰጪውን ምርቶች በማስተዋወቅ በሚሠራው ምርትን የማስተዋወቅ ስራ ውል ተቀባይ ባስገኘው ሽያጭ በድርጅቱ የገበያና የኮሚሸን ክፍያ የአሰራር ስልት መሰረት ኮሚሸን በወቅቱ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡

 

6.  ውልን ስለማቋረጥ

6.1.  ውልን ለማቋረጥ የሚበቃ በቂና አሣማኝ የስነምግባር፣ የውል እና የህግ ጥሰት ምክንያት መኖሩ ሲታወቅ ውል ሰጪም ሆነ ውል ተቀባይ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ወዲያውኑ ውሉን ማቋረጥ ይችላሉ፡፡

6.2. በቂና አሣማኝ ምክንያቶች የሚባሉት በዚህ ውል የተጠቀሡትና የውሉ አንቀፆች እና ከዚህ ውል ጋር አባሪ የሆነውን የድርጅት የአሠራር መመሪያዎች ተጥሰው ሲገኙ ነው፡፡ (የአሠራር መመሪያው በድርጅቱ ድህረ-ገጽ ላይ ተመላክቶ ይገኛል)፡፡

6.3. ዋነኛ የዚህ ስምምነት የውል አንቀፆች ጥሰት እና ወይንም የውል ሰጪም ሆነ የውል ተቀባይ መልካም ስም እና ዝና የሚያጎድፉ ወይንም ጉዳት የሚያደርሱ ድርጊቶችን መፈፀም ወይንም ሁለቱም ወገኖች በማናቸውም ምክንያት የ30 ቀን የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውሉን ለማቋረጥ ይቻላል፡፡

 

7.  ሚስጥር መጠበቅ

7.1.  በዚህ ውል የተመለከቱ ኃላፊነቶችን ለመወጣት ያስችል ዘንድ ውል ሰጪ ለውል ተቀባይ የሚሠጣቸው ሚስጥራዊ እና የወል ሰጪው ብቸኛ ባለቤትነት ያላቸውን መረጃዎች እንደሆነ ውል ተቀባዩ ያውቃል፡፡

7.2.  እነዚህን ሚስጥራዊ እና ውል ሰጪው ብቸኛ የባለቤትነት መብት የያዘባቸውን መረጃዎች ለሌሎች ሶስተኛ ወገኖች አሣልፎ መስጠት ወል ሰጪውን ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ውል ተቀባዩ ያውቃል፡፡

7.3.  ውል ተቀባዩ ለሚሰራው ስራ አስፈላጊ ለመሆኑ ምክኒያት እና በውል ሰጪው በግልፅ እና በፀሁፍ በተደረገ ስምምነት ካልሆነ በስተቀር ውል ተቀባይ ሚስጢራዊ የሆኑ እና የብቸኛ መብት ያላቸውን መረጃዎች ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ ወይንም መጠቀም ውሉ ፀንቶ ባለበት ጊዜም ይሁን ውሉ ከተቋረጠም በኃላ ፍፁም አይቻልም፡፡ ሚስጥራዊ መረጃ ወይንም ብቸኛ መብት ያላቸው መረጃዎች ከዚህ ሚከተሉትን ያካትታል፡፡

 

v   የተፃፈ፣ የታተመ፣ የንድፍ ስራ፣ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ምስል ወይንም ድምፅ በውል ሰጪው የተዘጋጀ እና ለውል ተቀባዩ የተላለፈ፤

v   ማንኛውም የተፃፈ ወይንም በግልፅ የሚታይ “ሚስጥራዊ” ወይንም ብቸኛ መብት የሚል የታተመበት ወይንም በተመሣሣይ ሁኔታ ወይንም በቢሮ ሁኔታ ውል ሰጪው ሚስጥር ብሎ የጠበቃቸውን እና የያዛቸው መረጃዎች

v   የአሰራር እና የሽያጭ እቅድ አፈፃፀም፣ የደንበኞች ዝርዝር፣ የአሰራር ስርዓት ፣ የንግድ ሚስጢር፣ ስነልኬት፣ ስነ ቀመር፣ የአሰራር ስልትና አካሄድ፣ የኮምፒውተር ፕጎግራም ወይንም ፈጠራ ወይንም ማንኛውም ማሻሻያ፣ የዋጋ ትመና እና የሽያጭ ቅድመ ትንተና፡፡

v   ውል ተቀባዩ በስራው ምክኒያት ካወቃቸው የውል ሰጪው ግለሰቦች ወይንም ደንበኞቻችን የሚመለከት ማንኛውም መረጃን ያጠቃልላል፡፡

በማንኛውም ሁኔታ ይህ ውል በሚቋረጥ ጊዜ ውል ተቀባይ ለስራው ያመቻው ዘንድ ከውል ሰጪ የተረከባቸው ማንኛውንም ንብረቶች ወዲያውኑ ለውል ሰጪ ያስረክባል፡፡

8.  ካሳ ክፍያን በተመለከተ

ውል ተቀባይ በዚህ ውል አፈፃፀም ሂደት ለሚያጠፋቸው ጥፋቶች ሁሉ ውል ሰጪው ላይ ላስከተለው ጉዳት ካሳ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡እንዲሁም ውል ሰጪ ውል ተቀባይ ምርቶቹን በማስተዋወቅ ላስገኘው ሽያጭ በገበያ ጥናቱና በኮሚሽ መክፈያ ስሌቱ መሰረት ተገቢ የሆነውን ኮሚሽን ወቅቱን ጠብቆ ይከፍላል፡፡ ምክኒያታዊ ያልሆነ የክፍያ ማዘግየት ቢኖር እና ውል ሰጪ ላይ በዚህ የክያ መዘግየት ምክኒያት የደረሰ ሊረጋገጥ የሚችል ጉዳት ቢኖር ውል ሰጪ ጉዳቱን የመካስ ሀላፊነት አለበት፡፡

9.  ግብር

ውል ተቀባይ ውል ሰጪው በግልፅ እና በፅሁፍ ሊከፍለው የተስማማበት ክፍያ ካልሆነ በስተቀር ውል ተቀባይ  ስራውን ለመስራት የሚያስፈልጉ ወጪዎችን እራሱ ይችላል፡፡ የውል ሰጪን ምርት በማስተዋወቅ ካስገኘው ሽያጭ ላይ 2% ቲን ሰርተፍኬት እና ፈቃድ ላላቸው 30% ደግሞ ቲን ሰርተፍኬት እና ፍቃድ ለሌላቸው ዊዝ ሆልዲንግ ታክስ ከሚከፈለው ኮሚሽን ላይ ውል ሰጪ  ቀንሶ ለመንግስት ገቢ ያደርጋል፡፡ ሌላ በሀገሪቱ የታክስ ህግ መሠረት ውል ተቀባይ  ሊከፍል የሚገባ ግብር ቢኖር የውል ተቀባይ  ግዴታ ይሆናል፡፡

10.    ተፈፃሚ ህጎች

በዚህ ውል ያልተካተቱ እና ለዚህ ውል አፈፃፀም አግባብነት ያላቸው በኢትዮጵያ የፍታብሔር ህግ ስለውሎች በጠቅላላው በሚለው ስር የተካተቱ አንቀፆች እንደ አግባብነታቸው ተፈፃሚ ይሆናሉ። በተጨማሪም የአዳዲስ ደንበኞችን ጥቅም ለማስጠበቅ ድርጅቱ የሚያወጣቸው የአሰራር መመሪያዎች ተፈፃሚነት ይኖራቸዋል።

11.    ማሻሻያ

ይህ ውል በውል እንደየአስፈላጊነቱ በይግዜው  ሊሻሻል ወይንም ሊለወጥ አይችልም፡፡

                  => ወደ ድርጅቱ በይነ መረብ ሲመዘገቡ ይህንን ውል አንብበው እና ተረድተው እንደተስማሙ ይቆጠራል፡፡

 

    

2023 © Etcareproduct.com